
የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል ከኪዩር ብላይንድነስ ከሚባል ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በተባበር ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ከጥቅምት 24 – 29 /2018 ዓ.ም ለ1730 የዓይን ህሙማን የዓይን ብርሃናቸው እንዲመለስ አደረገ።
የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል ከመደበኛ የዓይን ህክምና አገልግሎቱ ባሻገር በዓመት ከሁለት እስከ ሦስት ጊዜ ዘመቻ በማድረግ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ላለባቸው በርካታ ወገኖቻችን ነፃ የቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠት ህሙማን የዓይን ብርሃናቸው እንዲመለስ እያደረገ ይገኛል ።የዚህ የህክምና ዘመቻ ለየት የሚደረገው ከመቼውም በላይ ለማህበረሰባችን ተደራሽ ለማድረግ እና ጥራቱን የጠበቀ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት የደ/ወሎ



